በዚህ ሳምንት የነበሩ የሀገር ውስጥ የዝውውር መረጃዎች

 

ሀዲያ ሆሳዕና

ከቀናት በፊት አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለን ወደ ዋና አሰልጣኝነት የቀጠሩት ነብሮቹ 3 የአዳማ ተጫዋቾችን አስፈርመዋል እነዚህም

አዲስ ህንጻ (ኢትዮጵያ መድህን ፣ ንግድ ባንክ ፣ ደደቢት እና የሱዳኑ ሒላል ሸንዲ እንዲሁም አዳማ ከተማ መጫወቱ ይታወቃል)

ቴዎድሮስ በቀለ (መከላከያ እና አዳማ መጫወቱ ይታወቃል) {ሁለገብ ተከላካይ}

በረከት ደስታ (ከአዳማ ሁለተኛ ቡድን አደገ ከዛ እዛው አዳማ ከተማ መጫወት ጀመረ{የመስመር ተጫዋች}

ድሬዳዋ ከተማ

ሱራፌል ጌታቸውን አስፈርሟል (ሙገር ሲሚንቶ፣ ለአዲስ አበባ ከተማ፣ ለጅማ አባቡና፣ ለአዳማ ከተማ እና ለሀድያ ሆሳህና መጫወቱ ይታወቃል{ በአጥቂ አማካይ}

ወልቂጤ

ከቅዱስ ጊዮርጊስ አቡበከር ሳኒን ያስፈረሙት ክትፎዎቹ በሊጉ ልምድ አላቸው ተብሎ ከሚጠሩት የአማካይ ስፍራ አንዱ የሆነውን ፍሬው ሰለሞንን[ጣቁሩ] ከመከላከያ ማስፈረማቸው ይፋ ሆኗል ።{መከላከያ ፣ ሐዋሳ ከተማ እና ሙገር ሲሚንቶ መጫወቱ ይታወቃል}

ባህርዳር ከነማ

በአዳማ ከተማ ቤት ያለፉትን ዓመታት ማሳለፍ የቻለው የመሀል ተከላካዩ መናፍ ዓወል የጣና ሞገዶቹን የተቀላቀለ ሌላኛው ተጫዋች ሆኗል ።

ሌላኛው ተጫዋች ደግሞ ያለፉትን በርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ ቡና ቤት ማሳለፍ የቻለው አህመድ ረሺድ የጣና ሞገዶቹን ለመቀላቀል ተስማምቷል ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.