ሲዳማ ቡና ወልቂጤ ከተማን አሸነፈ።
ዛሬ ጥቅምት 15 ቀን 7:00 ሰዓት በተደረገ ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ሲዳማ ቡና በእንዳለ ከበደ የ82ኛ ደቂቃ ብቸኛ ግብ ወልቂጤ ከተማን 1 ለ 0 መርታት ችሏል።
በቀጣዩ 6ኛ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከአዳማ ከተማ ጥቅምት 28 ሰኞ 9:00 ሰዓት የሚጫወት ሲሆን ወልቂጤ ከተማ ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ቅዳሜ ጥቅምት 26 12:00 ሰዓት ላይ ይጫወታል።


