ተጠባቂው የአዲስ አበባ ደርቢ – ወቅታዊ መረጃ !

ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2018 የ20ኛ ሳምንት ተስተካካይ ጨዋታ – ተጠባቂው የአዲስ አበባ ደርቢ ሚያዝያ 18/2018 ከቀኑ 9 ሰዓት በአዲስ አበባ ስታዲየም ይደረጋል።

ስለጨዋታው ተጨማሪ መረጃዎች ፦

⚽️ በጨዋታው እለት የስታዲየም በሮች ከቀኑ 6 ሰዓት ጀምሮ ይከፈታሉ።

⚽️ ጨዋታው በOBN የቀጥታ ስርጭት ሽፋን ያገኛል።

⚽️ ከጨዋታው ቀደም ብሎ ከ6፡30 – 7፡20 የሁለቱ ክለቦች የቀድሞ ተጫዋቾች የወዳጅነት ጨዋታ ለ40 ደቂቃ ያደርጋሉ።

⚽️  ከክብር እንግዶች ፣ ከሁለቱ ተጋጣሚ ክለቦች ቦርድ አባላት፣ የተለየ ቪ.ቪ.አይ.ፒ(VVIP) ፍቃድ ከተሰጣቸው ተቋማት እና የሚድያ ባጅ(በተፈቀደ ቦታ) ውጪ ሌሎች የክቡር ትሪቡን ባጆች ጥቅም ላይ አይውሉም።

⚽️ ክቡር ትሪቡን በትኬት ለመግባት ሁለቱ ክለቦች ቀድመው የቆረጡት(Reserve) ትኬት እና ለሽያጭ የቀረቡ ውስን ትኬቶች ብቻ ጥቅም ላይ ይውላሉ።

⚽️ ጨዋታውን በስፖርታዊ ጨዋነት እንዲታደም መላው ደጋፊ ተጋብዟል።

Via Ethiopia Premier League Share Company

✍️ ዮናታን

Leave a Reply

Your email address will not be published.