የትግራይ ዋንጫ ዕጣ ማውጣት ስነ ሥርዓት ተካሂዷል
የትግራይ ዋንጫ ዕጣ ማውጣት ስነ ሥርዓት ዛሬ ተካሂዷል፡፡ ነገር ግን አነጋጋሪ የሆነው ጉዳይ የወልዋሎ በውድድሩ እንደሚሳተፍ መገለፅ ነው፤ ይህም ነገ በሚጀመረው የአዲስ አበባ ዋንጫ ላይ አስቀድሞ እንደሚሳተፍ ከመገለፁ በተጨማሪ በመጪው እሁድ ከኢትዮኤሌክትሪክ ጋር እንዲጫወት ፕሮግራም እንደወጣለት ይታወሳል፡፡
የትግራይ ዋንጫ በሁለት ምድቦች የተከፈለ ሲሆን ውድድሩንም በመጪው እሁድ ጥቅምት 30 ይጀምራል፡፡
ምድብ 1
⚽️ መቐለ
⚽️ ወላይታ ዲቻ
⚽️ ደደቢት
⚽️ አክሱም ከተማ
ምድብ 2
⚽️ ወልዋሎ
⚽️ ሲዳማ ቡና
⚽️ ስሑል ሽሬ
⚽️ ሶሎዳ አድዋ