መድፈኞቹ ነጥብ ጥለዋል።
መድፈኞቹ ነጥብ ጥለዋል
በአስራ ሶስተኛዉ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ መሪዎቹ አርሰናሎች ከ ሳውዝአምፕተን ጋር ነጥብ ተጋርተው ወጥተዋል ።
በጨዋታው ግራኔት ዣካ በ11′ ኛው ደቂቃ አስቆጥሮ ክለቡን መሪ ቢያደርግም በ65’ኛው ደቂቃ ላይ አርምስትሮግ አስቆጥሮ ሳውዝ አምፕተን ነጥብ ተጋርቶ እንዲወጣ አስችሎታል ።
አርሰናል በ28 ነጥብ አንደኛ ደረጃ ላይ ሲቀመጥ ሳውዝአምፕተን ደግሞ በ12 ነጥብ 15ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል ።
በቀጣይ የሊጉ መርሐ ግብር አርሰናል ከ ኖቲንግሀም ፎረስት እሁድ ጥቅምት 20 በ11 ሰአት እንዲሁም ሳውዝሀምፕተን ከ ክሪስታል ፓላስ ጋር ቅዳሜ ጥቅምት 19 በ11 ሰአት የሚጫወቱ ይሆናል።
በተመሳሳይ ሰዓት በተደረጉ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች
አስቶንቪላ 4-0 ብሬንትፎርድ
ሊድስ ዩናይትድ 2-3 ፉልሃም
ወልቩስ 0-4 ሌስተር ሲቲ



