የሜሲ እና ኪኬ ሲቲን የቃላት ጦርነት መርገብ ተስኖታል ፡፡

በላሊጋው የባለፈው የውድድር ዓመት ከ ሴልታ ቪጎ ጋር በባይላዶስ ያደረጉት ጨዋታ ለካታላኑ ክለብ ያሉበትን የውስጥ ችግሮች በገሀድ ያሳየ ሆኖ ማለፉ ይታወሳል ።
ለክለቡ ቅርበት ያላቸው ታማኝ የመረጃ ምንጮች እንደገለፁት በጨዋታው ሊዮኔል ሜሲ አሰልጣኙ ተጫዋቾቹን በተገቢው መንገድ እያያቸው እና እያናገራቸው እንዳልሆነ መናገሩ ተገልጿል ።
በዚህ ንግግር ደስተኛ ያልሆኑት የወቅቱ የክለቡ አሰልጣኝ ኪኬ ሴቲን ” ንግግሬ ደስተኛ ካለደረገህ የክለቡን መልቀቂያ በር የቱ ጋር እንዳለ ታውቀዋለህ ” የሚል ምላሽን መስጠታቸው ይፋ ሆኗል ።
ምንጭ ፡- sky sport
