ጉዳፍ ፀጋዬ ዘንድሮ የሚካሄደውን የአለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድሮች ላይ ሪከርዷን ታሻሽል ይሆን?

▪️ጉዳፍ ፀጋዬ የፊታችን የካቲት 9 በፈረንሳዩ ሊዬቪን ከተማ የሚካሄደው የአለም የቤት ውስጥ የአትሌቲክስ ውድድሮች እንደምትሳተፍ ታውቋል። የ24 አመቷ ጉድፍ ፀጋዬ ባሳለፍነው አመት በተካሄደው የአለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር በ 1500 ሜትር 3:53:09 በመግባት እና በ2014 በጀርመኗ ካርልስሩ ከተማ ጥሩነሽ ዲባባ ከገባችበት ሰአት 2 ሰከንዶችን አሻሽላ የአለም ሪከርዱን የግሏ ማድረግ ችላለች።ከዛም በሳምንቱ በ 800 ሜትር የግሏን ምርጥ ሰአት ማለትም 1:57:52 በመግባት ማጠናቀቋ እና አመቷን ደግሞ የነሀስ ሜዳሊያ በቶኪዮ ኦሎምፒክ በማግኘት አጠናቃለች።

▪️ይህ የአለም የቤት ውስጥ አትሌቲክስ ውድድር አምና ድንቅ እንቅስቃሴ ያደረጉትን በ 1500 ሜትር ኖርዌያዊው jakob ingebrigsten እና በ 3000 ሜትር ኢትዮጵያዊ ጌትነት ዋሌ ጨምሮ የ100 ሜትር የኦሎምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤቱን ጣልያናዊው ማርሻል ጄኮፕሰን ጨምሮ ሌሎችም በውድድሩ ምንመለከታቸው አትሌቶች ናቸው።

ፈለቀ ደምሴ

Michael dejene

Michael dejene Bsc in computer science Born in october 12,1998 Age 23 Editor of ethiopianssport.com

Leave a Reply

Your email address will not be published.