ኢትየጵያውያን በሮም በድል ተንበሸበሹ

▪️የሮም ማራቶን።

▪️እኤአ በ1995 የጀመረው እና ዘንድሮ ለ27 ጊዜ የተካሄደው የማራቶን ውድድር በውብ መልከአ ምድር እንዲሁም በሰው ሰራሽ ቅርሶቿ የምትታወቀው የጣልያኗ ዋና ከተማ ሮም ተካሂዷል።

▪️በአለምአፉ የአትሌቲክስ አወዳዳሪ አካል የብር ደረጃ የተሰጠው ይህ ውድድር ዘንድሮም ከ10,000 በላይ ተሳታፊዎችን አካቷል።

▪️በሴቶች አትሌት ሴቻለ ደለሳ አዱኛ 2:26:08 በሆነ ጊዜ በቀዳሚነት ስትገባ ኬንያዊቷ አትሌት ግላዲስ ጄሩቶ በ2:28:46 በሆነ ሰዓት ሁለተኛ እንዲሁም ኢትዮጵያዊቷ አትሌት ታደለች ነዲ በ2:31:00 ሰዓት በመግባት ሶስተኛ ወጥታለች።

▪️በወንዶች ደግሞ አኢትጵያዊው አትሌት  ፍቅሬ በቀለ ተፈራ የቦታውን ክብረወሰን በማሻሻል በ2:06:48 በሆነ ሰዓት በመግባት በቀዳሚነት ውድድሩን አጠናቋል። ታደሰ ማሞ 2:07:04 ሁለተኛ እንዲሁም ሌላው ኢትዮጵያዊ አትሌት አብርሀም ግርማ በቀለ 2:08:31 በመግባት 3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል።

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.