እግር ኳስ ንጉሷን አጣች

በአለማችን እግር ኳስ ላይ መንገስ የቻለው አርጀንቲናዊው ምትሀተኛ ዲዬጎ አርማንዶ ማራዶና ዛሬ አመሻሹ ከዚህ አለም በሞት ተለየ ።

በርካታ የዲያጎ አርማንዶ ማራዶናን እና የብራዚላዊው ጥበበኛ ፔሌን አድናቂዎች ሁለቱን የአለም እግር ኳስ ንጉሶችን በማወዳደር ሰጣገባ ውስጥ ሲገቡ እንመለከታለን ።

የአርጀንቲና ኮከብ ተጫዋች ከመሆኑም ባለፈ የሀገሩ አርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የነበረው ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና በመኖሪያ ቤቱ ውስጥ ሳለ በልብ ችግር ነበር ይቺን አለም የተሰናበትው ።

ማራዶና በዚህ ወር መጀመሪያ አካባቢ ነበር በአንጎሉ ውስጥ ላጋጠመው የደም መርጋት የተሳካ ቀዶ ሕክምና ተደርጎለት የነበረ ሲሆን በተከታይነትም ከአልኮል ሱስ ለመላቀቅ ሕክምና ሲደረግለትም ቆይቶ ነበር ።

ዲያጎ አርማንዶ ማራዶና በተወለደ በ60 አመቱ ነው ላይመለስ ያሸለበው ። 🕯🕯🕯

Leave a Reply

Your email address will not be published.